የልደታ ክ/ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት በተሻሻለው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 84/2016 መሰረት የሚከተሉት ስልጣንና ኃላፊነት ይኖሩታል
- ተጠሪነታቸው ለእርሱ የሆኑ አስፈጻሚ አካላትን በበላይነት ይመራል፤ ያስተባብራል፤ ይቆጣጠራል፤
- ዕቅድና በጀት ከከተማው ስራ አስኪያጅ ጋር በመመካከር በማዘጋጀት ለክፍለ ከተማው ዋና ሰራ አስፈፃሚ ያቀርባል፣ሲፀድቅም ተግባራዊ መሆኑን ያረጋግጣል
- የስራ አፈፃፀም ሪፖርቱን አዘጋጀቶ ለከተማው ስራ አስኪያጅና ለክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ያቀርባል
- በቻርተሩ የተሰጡትን ሌሎች ሥልጣንና ተግባራት እንዲሁም በክፍለ ከተማው የሚሰጡትን ተግባራት ያከናውናል
- ለክፍለ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት በተጨማሪ እንዲሰራቸው በአዋጅ ቁጥር 74/2014 ዓ.ም እንዲካተቱ ታሳቢ የተደረጉ ስልጣንና ተግባራትን ያከናውናል